ትምህርት ከጴጥሮስ መልእክቶች (I) << >> መቅድም ደቀ መዝሙሩ ጴጥሮስ ያጋጠመውን ዓይነት ሁኔታ ያላጋጠመው ማን አለ? የእርሱ ሰብአዊነት ሁላችንም ቢያንስ በሆነ መንገድ ልንገናኝበት የምንችልበት ነው። የእርሱ ቅንዓትና የጌታውን ትዕዛዝ ለማድረግ ዝግጁነቱ አበረታች ነው። በርግጠኝነት አልፎ አልፎ ለሚፈጽመው አሳፋሪ ስህተቱ ልንረዳውና ከውድቀት በኋላ እንደገና በሚነሳበት መንገድ ልንበረታታ እንችላለን። ጴጥሮስ በእግዚአብሔር መሪነት ያሳለፈው የብስለት ሂደት በቅዱሱ የጽሑፍ ውስጥ ሊቀመጡ የሚገባቸው ሁለት መልእክቶች ይዞ ወደ ተከበረ ሐዋርያነት አመጣው። በእነዚህ ምክንያቶች፣ በሚቀጥሉት ሶስት ወራት፣ በአለም ዙሪያ ያሉ የሰንበት ትምህርት ተማሪዎች ትምህርት ከጴጥሮስ መልእክት (I) ትምህርቶች ላይ ትኩረት ያደርጋሉ። በዚህ የእግዚአብሔር መንፈስ መሪነት የተገኘ የበለጸጉ የእውነት ዕንቁዎች የተጻፉት በአስቸጋሪ ጊዜያት ከጌታ ጋር መሄዳችንን ለማጠናከር ነው። በጴጥሮስ መልእክት ውስጥ ካሉት ቁልፍ ነጥቦች አንዱ የእግዚአብሔር ሰዎች በኃጢአት ለጨለመው ዓለም ብሩህ ምስክር እንዲሆኑ የክርስቶስን አካል የሚገነቡ ሕይወቶች መሆን አለባቸው። “በመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ሥር መነቃቃት (ሪቫይቫል) እና ተሐድሶ መደረግ አለባቸው። መነቃቃትና ተሀድሶ ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው። መነቃቃት የመንፈሳዊ ህይወት መታደስን፣ የአዕምሮ እና የልብ ሀይልን ማደስን፣ ከመንፈሳዊ ሞት መነሳትን ያመለክታል። ተሐድሶ እንደገና ማደራጀትን፣ የሃሳቦችንና የንድፈ ሃሳቦችን ፣ ልምዶችን እና ልምምዶችን መለወጥን ያመለክታል። ተሐድሶ ከመንፈስ መነቃቃት ጋር ካልተገናኘ የጽድቅን መልካም ፍሬ አያፈራም። መነቃቃት እና ተሐድሶ የተሰጣቸዉን ሥራ መሥራት አለባቸው፤ ይህን ሥራ ሲሠሩ ደግሞ መዋሄድ አለባቸው።”—Selected Messages. bk. 1, p. 128. የጴጥሮስን የመጀመሪያ መልእክት ስናጠና ሁላችንም ለመንፈሳዊ እድገታችን የሚሆን ነገር መቃረም እንደንችል ለእያንዳንዳችን አንድ አስደሳች ምስክርነት ጠንካራ ፍላጎትን ያነሳሳልናል፡- “ወንድሜ፣ ብትፈቅድ በእግዚአብሔር ጠንካራ ሰው መሆን ትችላለህ። ለአገልግሎቱ እንዲቀደሱ እግዚአብሔር እንዲጠብቁ በአደራ የሰጣችሁ የመክሊት ችሎታዎች አሏችሁ። ነገር ግን ሁሉንም ለክርስቶስ ካልተገዛህ፣ ችሎታህ ለራስህም ሆነ ለሌሎች አደገኛ ይሆናል፣ ይህም ሌሎች ከእውነት ርቀው ከክርስቶስ እንዲርቁ ይመራቸዋል። “በውስጡ ያሉ የቤተክርስቲያኑ አባላት—በጣም ብዙ ሊደረግላቸው ይገባል። ለክርስቶስ የጋለ ቅንዓት ሊኖራቸው ይገባል፣ የበለጠ ትሁት፣ የበለጠ ታጋሽ፣ የበለጠ ደግ ፣ የበለጠ መማር የሚችሉ፣ በሁሉም ረገድ ክርስቶስን የሚመስሉ መሆን አለባቸው። በባህሪያቸው የጸጋን የመቀደስ ኃይል ለዓለም ሊገልጹ ይገባቸዋል። በትእዛዛት ወይም በምሳሌ፣ ለዚህ አስፈላጊ ስራ እንቅፋት እንዳንሆኑ እግዚአብሔር ይጠብቀን። ከየሱስ ጋር ትሰራለህን? ለገዛህ ጌታ እውነተኛ ትሆናለህን? ሁሉንም ጥቃቅን ጉዳዮችን ትተዋለህን? ወደ ትልቅ እምነት፣ ወደ ትልቅ በጎ አድራጎት መሳብ አለቦት። ዘላለማዊ ጠቀሜታ ላላቸው ነገሮች የበለጠ አክብሮት ያስፈልጋችኋል።”— Testimonies for the Church, vol. 5, pp. 570, 571 ይህንን ስናጠና ሁላችንም ልብ እንድንል ጌታ ይርዳን! የጄነራል ኮንፈረንስ ሰንበት ትምህርት ቤት መምሪያ << >>