Back to top

Sabbath Bible Lessons

ወንጌል እንደ ዮሐንስ መሠረት (ፍል ሁለት)

 <<    >> 
8ኛ ትምህርት ሰንበት፣ ግንቦት 16፣ 2017

የሱስ እና አብርሃም

የመታሰቢያ ጥቅስ፡- “አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሤት አደረገ፥ አየም ደስም አለው።” (ዮሐ. 8፡56)።

“[አብርሃም] ከመሞቱ በፊት መሲሑን ለማየት ይችል ዘንድ ከልቡ ጸለየ። ክርስቶስንም አየ።”—The Desire of Ages, p. 468.

ለንባብ የተመረጠዉ መጽሐፍ፡   Christ’s Object Lessons, pp. 269–271, 330–332; Early Writings, pp. 149–153. 

እሁድ ፣ ግንቦት 10

1. የአብርሃም ልጆች

ሀ. ፈሪሳውያን ያለማቋረጥ የሚናገሩት ነገር ምንድን ነው? ዮሐንስ 8:33፣ 39 (የመጀመሪያ ክፍል) ግን እንዲህ ዓይነቱን ግንኙነት ማረጋገጥ የሚቻለዉ በምንድነው? ዮሐንስ 8፡39 (የመጨረሻው ክፍል)፣ 56፤ ሮሜ 9፡6-8

“ፈሪሳውያን የአብረሃም ልጆች ነን ባዮች ነበሩ። የሱስ ግን ያ መብት ሊኖራቸው የሚችለው የአብርሃምን ሥራ ሲሠሩ ብቻ መሆኑን ነገራቸው። እውነተኛ የአብርሃም ልጆች የሆኑ ሁሉ እርሱ እንዳደረገው ለእግዚአብሔርታዛዥ የሆነ ሕይወት ይኖራሉ እንጂ ከአግዚአብሔር የተሰጠውን እውነት የሚናገርን ሰው ሕይወት ለማጥፋት አይሞክሩም። እነዚያ የኦሪት ሕግ ሊቃውንት በክርስቶስ ላይ ሲያሴሩ የአብርሃምን ሥራ መሥራታቸው አልነ በረም። በትውልድ ብቻ የአብርሃም ዘር መሆን ምንም ፋይዳ የለውም። እነዚህ ሰዎች የአብርሃም መንፈስ እንዲያድርባቸውና የእርሱንም ሥራ እንዲሠሩ የሚያደርጋቸው ከእርሱ ጋር የሚያስተሳስራቸው መንፈሳዊ ግንኙነት እስካልኖራቸው ድረስ የአብርሃም ልጆች ሊሆኑ አይችሉም።

“ይህ መርሖ የክርስቲያኑን ዓለም ለረጅም ዘመን ሲያነታርክ ለኖረው የቤተ ክርስቲያን የመሪነት ሥልጣን አወራረስ ጥያቄ መፍትሔ ነው። የአብርሃም ዘር መሆን የሚረጋገጠው በስምና በሥጋ ትውልድነት ላይሆን በባሕርይ ተመሳሳይነት ነው። እንደዚሁም የቤተ ክርስቲያን የመሪነት ሥልጣን አወራረስ የሚመሠረተው በሥልጣን ማስተላለፍ ላይ ሳይሆን በመንፈሳዊ ግንኙነት ላይ ነው። የሐዋርያትን ሥልጣን ለመረከብ ብቁ የሚያደርገው በሐዋርያት መንፈስ የታነጸ ሕይወትና እነርሱ ባስተማሩት እውነት ማመን ነው። ሰዎችን የመጀመሪያዎቹ የወንጌል መምህራን ተተኪ ለመሆን የሚያበቃቸው ይህ ነው።”—The Desire of Ages, pp. 466, 467.


ሰኞ ፣ ግንቦት 11

2. ነን ብለዉ የሚኩራሩበትን አይደሉም

ሀ. አይሁዳውያን የአብርሃም ዘር ቢሆኑም፣ ክርስቶስን ሲቃወሙ የማን ልጆች ሆኑ? ዮሐንስ 8፡41-44

“የሱስ የአይሁዶችን የአብርሃም ልጅነት አላመነም። «እናንተ የምትሠሩት የአባታችሁን ሥራ ነው» አላቸው። እነርሱም በማፌዝ «እኛ በምንዝር የተወለድን ዲቃላዎች አይደለንም፣ አንድ አባት አለን፣ እርሱም እግዚአብሔር ነው» ሲሉ መለሱለት። እነዚህ ቃላት የየሱስን የአወላለድ ሁኔታ የሚነኩ ሲሆኑ በእርሱ ለማመን የጀመሩት ሰዎች በሚገኙበት የሱስን ለመበከል የተሰነዘሩ ነበሩ። የሱስ ግን የሰነዘሩበትን ጸያፍ የአሽሙር አነጋገርከምንም ሳይቆጥር «እግዚአብሔር አባታችሁ ቢሆንማ እኔን በወደዳችሁኝ ነበር፣ ምክንያቱም እኔ እዚህ ያለሁት ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቼ ነው» አላቸው።

“የእነዚህ ሰዎች ሥራ ሐሰተኛና ነፍስ ገዳይ ከሆነው ከሰይጣን ጋርየነበራቸውን ግንኙነት ይመሰክራል። ስለዚህ የሱስ «እናንተ የአባታችሁ የዲያብሎስ ልጆች ናችሁ። ፍላጐታችሁም የአባታችሁን ምኞት መፈጸም ነው። እርሱ ከመጀመሪያ አንሥቶ ነፍሰ ገዳይ ነበረ። እውነት በእርሱ ስለሌለ ከእውነት ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ... እኔ ግን እውነትን የምናገርስለሆንሁ አታምኑኝም» ሲል ነገራቸው። ዮሐ.8:44፣45። የሱስ በአይሁድ መሪዎች ዘንድ ተቀባይነትን ያላገኘበት ምክንያት እውነትን በእርግጠኛነት ስለተናገረ ነው። እነዚያ እራሳቸውን ጻድቅ አድርገው ይቆጥሩ የነበሩት ሰዎች ያኮረፉት እውነቱ ስለተነገራቸው ነው። እውነት ስሕተታቸውን ስላጋለጠ፣ ትምህርታቸውንና ድርጊታቸውንም ስላወገዘ ተቀባይነት አጣ። ስሕተታቸውን አምነው ንስሐ ለመግባት እራሳቸውን ዝቅ ከማድረግ ይልቅ እውነትን ላለማየት ዓይኖቻቸውን መሸፈን መረጡ። ለእውነት ፍቅር አልነበራቸውም። እውነቱን ቢያውቁም የመቀበል ፍላጐት አልነበራቸውም።”—The Desire of Ages, p. 467.

ለ. የአብርሃም ልጆች የሚያደርገን ምንድን ነው? የአይሁድ መሪዎችስ እውነተኛ የአብርሃም ልጆች እንዳልሆኑ ያሳዩት እንዴት ነው? ገላትያ 3:6–9ዮሐንስ 8፡40

“እናንተ ግን አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ ዳግመኛ ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና።” የባርነት መንፈስ የሚመነጨው በወግ (በስማዊ) ሀይማኖት መሰረት ለመኖር በመፈለግ የህግ ጥያቄዎችን በራሳችን ሃይል ለማሟላት በመታገል ነው። ለእኛ ተስፋ ያለን በአብርሃም ቃል ኪዳን ሥር ስንሆን ብቻ ነው፤ እርሱም በክርስቶስ የሱስ በማመን የሚገኘው የጸጋ ቃል ኪዳን ነው። ለአብርሃም የተሰበከለት፣ በእርሱም ተስፋ ያገኘበት ወንጌል ዛሬ ለእኛም የተሰበከልን፣ በእርሱም ተስፋ ያለንበት ወንጌል ነውና። አብርሃም የሱስን ተመልክቶ ነበር፤ እርሱም የእምነታችን ጀማሪና ፈጻሚ ነው።”—The Youth’s Instructor, September 22, 1892


ማክሰኞ ፣ ግንቦት 12

3. የክርስቶስ ባሕርይ

ሀ. የየሱስ ጠላቶች ከነቁጣ አልባ ባሕርይው ጋር በተያያዘ መመለስ ያልቻሉት ጥያቄ ምንድነው? ዮሐንስ 8፡46 (የመጀመሪያ ክፍል)።

“ለአባቱ ትእዛዝ ፍጹም በመታዘዝ፣ በምድራዊ ህይወቱ ክርስቶስ ፍጹም ባህርይን አዳበረ። በሰው አምሳል ወደ ዓለም በመጣ ጊዜ፣ ለሕግ ተገዥ ሆኖ፣ ለሰዎች ሕመማቸውን፣ ሐዘናቸውን፣ በደላቸውን እንደተሸከመ ሲገለጥ፣ በአንዳች ነጥብም ግን ኃጢአተኛ አልሆነም። ከፈሪሳውያን በፊት 'ከእናንተ ስለ ኃጢአት የሚወቅሰኝ ማን ነው?' ማለት ችሏል፡፡ በእርሱ ላይ አንድም የኃጢአት እድፍ አልተገኘበትም። ነውር የሌለው የእግዚአብሔር በግ ሆኖ በዓለም ፊት ቆመ።”—Sons and Daughters of God, p. 25.

“የሱስ በሰማይ፣ ባልወ ደቁት ዓለማትና በኃጢአተኛ ሰዎች ፊት ሕግን አክብሮ ኖረ። በመላእክት፣ በሰዎችና በአጋንንት ፈት ማንም ሊያስተባብለው በማይችል አኳኋንና በሌላ ሰው አንደበት ቢነገር የእግዚአብሔርን ስም እንደማርከስ የሚያስቆጥረውን «ዘወትር የማደርገው እርሱን (እግዚአብሔርን) ደስ የሚያሰኘውን ነገር» ነው ብሎ ለመናገር ቻለ።”—The Desire of Ages, p. 467, 468

ለ. የሱስ የሰው ልጅ ተብሎ ከተነገረው በተጨማሪ ቅዱሳት መጻሕፍት ስለ ክርስቶስ ባሕርይ ምን ይናገራሉ? ዕብራውያን 4:15፤ 1ኛ ጴጥሮስ 1:18፣ 19

“ሰዎች በክርስቶስ እንደ መሲህ አድርገው ያመኑት በሚታዩ ማስረጃዎች የተነሳ ወይም ከደም ግባቱ የተነሣ አልነበረም፣ ነገር ግን በሌላ በማንም ሊገኝ በማይችል በእርሱ ውስጥ ብቻ በተገኘው ከላቀ የጠባይ ባሕርይ የተነሳ ነው እንጂ።”—The SDA Bible Commentary [E. G. White Comments], vol. 7, p. 904.

ሐ. በየሱስ ሕይወት እንዴት ልንነካ ይገባናል? ፊልጵስዩስ 2፡6-8

“አርአያችን እኛን ለማዳን አስቸጋሪውን፣ እራስን የመካድና የመስዋዕትነት እንዲሁም የትህትና መንገድ አልሄደምን? እሱን ችግሮች አጋጥመውታል፣ የሚያበሳጩ ነገሮች አጋጥመውታል፣ እንዲሁም እኛን በማዳን ስራው ነቀፋና ስቃይ ደርሶበታል። ታዲያ የክብር ንጉስ እንድንሄድበት የመራንን መንገዱን ለመከተል እንቢ እንበልን? የቤዛችን መከራ ስናስታውስ በራሳችን የሥራ ድርሻ ውስጥ ስለሚደርስብን ችግር እና ፈተና ሊናማርር ይገባናል?”—Tes¬timonies for the Church, vol. 3, p. 371.


ረቡዕ ፣ ግንቦት 13

4. የክርስቶስ ተከታዮች ባሕርይ

ሀ. የሁሉም እውነተኛ የክርስቶስ ተከታዮች ዓላማ ምንድን ነው? 1ኛ ጴጥሮስ 1:13-16

“የእኛ ሥራ በተግባራችን መስክ ክርስቶስ በምድር ላይ በነበረው ሕይወት በእያንዳንዱ የባሕርይ ደረጃ ያገኘውን ፍጽምና ለማግኘት መጣር ነው።”—That I May Know Him, p. 130..

ለ. እዚህ ግብ ላይ እንዴት መድረስ እንችላለን? ዕብራውያን 12:1-4ገላትያ 5:6 (የመጨረሻው ክፍል)፤ ፊልጵስዩስ 3:12–15፤ 4፡13።

“ታላቁ መምህራችን የጌታችንና የመድኃኒታችን የየሱስ ክርስቶስ ፍጽምና ደረጃ ላይ መድረስ የምንችለው እንዴት ነው? የእሱን መስፈርት ማሟላትና ይህን ያህል ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረስ እንችላለንን? አዎ እንችላለን፣ ያለበለዚያ ክርስቶስ እንዲህ እንድናደርግ ባላዘዘን ነበር። እርሱ ጽድቃችን ነው። በሰብአዊነቱ ከኛ በፊት ተመላልሶ የባህርይ ፍፁምነትን የምናገኝበትን መንገድ አሳየን። በፍቅር በሚሰራና ነፍስን በሚያነጻ በእርሱ ላይ እምነት ሊኖረን ይገባል። የባህሪይ ፍፁምነት ክርስቶስ ለእኛ በሆነው ላይ የተመሰረተ ነው። በአዳኛችን ትሩፋቶች ላይ የማያቋርጥ ጥገኛ ከሆንን እና የእርሱን ፈለግ ብንከተል እንደ እርሱ ንጹሕና ርኩሰት የሌለን እንሆናለን።”—Ibid

ሐ. በእግዚአብሔር ፊት ንጹሕና እንከን የለሽ መሆን የምንችለው እንዴት ነው? ሮሜ 5፡18-20፤ ዕብራውያን 10፡14

“ክርስቶስ ከተጸጸቱት በስተቀር ማንንም ይቅር አይልም፣ ይቅርታ የሚያደርግለትን ሰው ግን አስቀድሞ እንድጸጸት ያደርገዋል።”—Selected Messages, bk. 1, pp. 393, 394.

“ኃጢአተኛው ወደ ቀራንዮ ይመለከት፤ ልክ ህጻን ልጅ ባለ እምነት፣ ጽድቁን በመቀበል እና በምህረቱ በማመን፣ በክርስቶስ ትሩፋት ላይ ማረፍ አለበት፡፡ . . .

“ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ እንዲሞት የሚያደርግ ይህ—እንዴት የሚያስደንቅ፣ የማይመረመር ፍቅር—ምን ዓይነት ፍቅር ነው! የሕጉን ጠንከር ያለ የይገባኛል ጥያቄዎችን የምትረዳ ነገር ግን እጅግ የሚበዛውን የክርስቶስን ጸጋ ገና ያልተረዳች ነፍስ እንዴት ያለ ኪሳራ ላይ ናት!”—Ibid., p. 384.


ሐሙስ ፣ ግንቦት 14

5. ባህሪያችን ልክ እንደ እሱ ይሆናል

ሀ. ጥሪያችንን እና መመረጣችንን እንዴት እናረጋግጣለን? 2ኛ ጴጥሮስ 1:4-11፤ ራእይ 19፡8።

“ያኔ እግዚአብሔር ከአዳም የፈለገውን ዓይነት ፍጹም መታዘዝን፣ እንከን የለሽ ጽድቅን፣ በዓይኑ ፊት ጉድለት የሌለበት ሆኖ መገኘትን ዛሬም ይፈልግብናል፡፡ ሕጉ የሚፈልገውን ሁሉ ማድረግ እንድንችል እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ የክርስቶስን ጽድቅ ወደ ዕለታዊው ተግባር ማምጣት የሚችል እምነት ከሌለን በስተቀር ይህን ማድረግ አንችልም።”—Selected Messages, bk. 2, p. 381.

“ሰይጣን እስከነገሰ ድረስ፣ ሕይወታችንም እስካለች ድረስ፣ ልንገዛው የሚገባን ራስ፣ ልናሸንፈው የሚገባን የኃጢአት ዝንባሌ አለ፣ ይህንን ማድረግ የምናቆምበት ቦታ አይኖርም፣ ሙሉ በሙሉ ደረስኩበት የምንልበት ነጥብም የለም። መቀደስ የዕድሜ ልክ ታዛዥነት ውጤት ነው።”—The Acts of the Apostles, pp. 560, 561.

“በእርሱ በማመን የመለኮታዊ ተፈጥሮ ተካፋዮች መሆን እና በዓለም ካለው በፍትወት ከመበስበስ ማምለጥ ዕድላችን እንደሆነ ልንገነዘብ ይገባል። ያኔ ከኃጢያት ሁሉ፣ ከባሕርይ ጉድለት ሁሉ እንነጻለን። አንድም የኃጢያት ዝንባሌ ልንይዝ አይገባንም። . . .

“ከመለኮታዊ ተፈጥሮ ስንካፈል፣ በዘር የሚተላለፍና ያዳበርነውን የኃጢአት ዝንባሌዎች ከባህሪያችን ይቆረጣሉ፣ እንዲሁም ለበጎ ነገር ሕያው ኃይል እንሆናለን። ስለ መለኮታዊው መምህር ስንማር፣ በየቀኑ ከእርሱ ተፈጥሮ ተካፋይ በመሆን፣ የሰይጣንን ፈተናዎች በማሸነፍ ከእግዚአብሔር ጋር እንተባበራለን። ክርስቶስ ከእግዚአብሔር ጋር አንድ እንደሆነ ሰው ከክርስቶስ ጋር አንድ እንዲሆን እግዚአብሔር ይሠራል፣ ሰውም ለዚህ ዓላማ ይሠራል። . . .

“የማሸነፍ ኃይልን የሚሰጠን እግዚአብሔር ነው። ቃሉን የሚሰሙና ትእዛዛቱን የሚታዘዙ ሰዎች ጻድቅ ባሕርያትን ለመመስረት ያስችላቸዋል።”—The SDA Bible Commentary [E. G. White Comments], vol. 7, p. 943.


አርብ ፣ ግንቦት 15

የግል ግምገማ ጥያቄዎች

1. ፈሪሳውያን በዘር ሀረጋቸው ላይ ተመስርተው የዘላለም ሕይወት ሊያገኙ ያልቻሉት ለምንድን ነው? ወይም ዛሬም ቢሆን የትኛውም ሰው ዘራቸውን ወይም ዲኤንኤ (ዘረመላቸውን) የመዳን ምልክት አድርገው ማመን የማይቻሉት ለምንድነው?

2. የአብርሃምን እውነተኛ ልጆች ባህሪያት ግለጽ።

3. የሱስ ስለ ባህሪይው ምን ማለት ችሏል?

4. በእያንዳንዱ ክርስቲያን ፊት ምን ዓላማ ተቀምጧል?

5. በእግዚአብሔር ፊት ፍጹምና ነውር የሌለን ሆነን ልንገኝ የምንችለው እንዴት ነው?

 <<    >>